Fana: At a Speed of Life!

በምስራቅ ጎጃም ዞን አዋበል ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 14 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን አዋበል ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡

አደጋው ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ዶልፊን የህዝብ ማመላለሻ መኪና በየከይት ቀበሌ ከሌሊቱ 9 ሰዓት ከ 40 አካባቢ በመገልበጡ የደረሰ ነው ተብሏ፡፡

በዚህም የሁለት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን አራት ሰዎች ላይ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል፡፡

ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎችም በሉማሜ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን ከአዋበል ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ከፌስቡክ ገፃችን በተጨማሪ ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
የፋና ድረ ገጽ https://www.fanabc.com/ ይጎብኙ፤
ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለማግኘት የፋና ቴሌቪዥን የዩቲዩብ ቻናል https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/ ሰብስክራይብ ያድርጉ
ፈጣን መረጃዎችን ለማግኘት ትክክለኛውን የፋና ቴሌግራም ቻናል https://t.me/fanatelevision ይቀላቀሉ
ከዚህ በተጨማሪም በትዊተር ገጻችን https://twitter.com/fanatelevision ይወዳጁን
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.