ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ ከቻይናው የኢኮኖሚና ንግድ ጉዳዮች ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 29 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ለሊሴ ነሜ ከቻይናው የኢኮኖሚና ንግድ ጉዳዮች ሚኒስትር ከሆኑት ያንግ ዪ ሃንግ ጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይቱ የኢትዮጵያ የንግድ ዘርፍ በማሻሻል ባለሃብቶችን የመሳብ እና የማሳደግ ስራን መስራት፣ የሴክተሩን ሰው ሃብት በጋራ የማልማት ስራዎች ዙሪያ መክረዋል፡፡
እንዲሁም የኢትዮጵያን ኢንቨስትመንት አማራጮች ለቻይና ባለሃብቶች በጋራ የማስተዋወቅ ስራ ዙሪያም መወያየታቸውን ከኢንቨስትመንት ኮሚሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!