Fana: At a Speed of Life!

በሐረሪ ክልል የብልጽግና ፓርቲ ሕዝባዊ የውይይት መድረክ በመካሄድ ላይ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል በብልጽግና ፓርቲ ጉባዔ ውሳኔዎችና ቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ የሚመክረው የህዝብ የውይይት መካሄድ ጀምሯል፡፡
ህዝባዊ መድረኩ የፈተናዎች ብዛት ከብልፅግና ጉዟችን አያስቀረንም በሚል መርህ ቃል ነው እየተካሄደ የሚገኘው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦድሪን በድሪ፥ ህዝባዊ መድረኩ የዜጎች ጥያቄ የሚስተጋባበት መሆኑን ገልፀዋል።

ርዕሰ መስተዳደሩ አያይዘውም ባለፉት ስድስት ወራት የህዝቡን ጥያቄ የሚመልሱ የተለያዩ ስራዎች መሠራታቸውን ተናግረዋል።

የብልፅግና ፖርቲ የህዝቦችን በጋራ የመኖር እሴትን ለማጠናከር እየሰራ የሚገኝ ፖርቲ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የብልፅግና ስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑት አቶ ሞገስ ባልቻ ናቸው።

በዚህም ፖርቲው በመስራች ጉባሄው ያሳለፋቸውን የዜጎችን የመልካም አስተዳደር፣ የዴሞክራሲና የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ ህዝባዊ ውይይት ማድረግ አስፈልጓል ብለዋል።

ከዋጋ ግሽበት ጋር ተያይዞ የተከሰተውን የኑሮ ውድነት ለመፍታት ዓለም አቀፋዊ ሁኔታዎች፣ የንግድ ስርዓትንና የሀገር ውስጥ ምርቶች ላይ በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።

በመድረኩ የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦድሪን በድሪን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ የሃይማኖት መሪዎችና የፖርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተሳታፊዎች ናቸው።

በእዮናዳብ አንዱዓለም

 
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.