Fana: At a Speed of Life!

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት መደበኛ ጉባዔ እየተካሄደ ነው፡፡

ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት በሚያካሂደው ጉባዔው÷ የ12ኛ መደበኛ ጉባዔ ቃለ ጉባዔ እና የክልሉን የአስፈጻሚ አካላት የ2014 ዓ.ም የ6 ወር ሪፖርት በማድመጥ መርምሮ ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተጨማሪም በወቅታዊ ሀገራዊና ክልላዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት ማድረግን ጨምሮ በ8 የተለያዩ አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን እንደሚያልፍም ይጠበቃል፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሃሰን የክልሉን የአስፈጻሚ አካላት የ2014 ዓ.ም የ6 ወራት አፈጻጸም እያቀረቡ መሆኑን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.