Fana: At a Speed of Life!

የደቡብ ኮሪያ፣ የጃፓን እና አሜሪካ የጦር ባለሥልጣናት በቀጠናዊ የፀጥታ ጉዳይ ላይ ሊመክሩ ነው

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 20 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ኮሪያ ጦር አዛዥ ዎን ኢንቾል እንዲሁም የአሜሪካ እና የጃፓን አቻዎቻቸው ማርክ ሚሊ እና ኮጂ ያማዛኪ በነገው ዕለት በቀጠናዊ የደኅንነት ጉዳዮች ላይ እንደሚመክሩ ተገለጸ፡፡

የጦር አዛዦቹ በሃዋይ ተገናኝተው እንደሚመክሩ ሲ ጂ ቲ ኤን በዘገባው አመላክቷል።

በውይይታቸው የኮሪያን ባሕረ – ሠላጤ እና የሰሜን ምሥራቃዊ እስያ ቀጠናዎችን ደኅንነት እና ፀጥታ በትብብር ማረጋገጥ በሚቻልበት ጉዳይ ላይ ይመክራሉ ተብሏል።

ዘ ኮሪያ ሄራልድ በዘገባው እንዳመላከተው የሀገራቱ የጦር ባለሥልጣናት በጉዳዩ ላይ ለመነጋገር የቀጠሩት ባሳለፍነው ሐሙስ ሰሜን ኮሪያ አኅጉር አቋራጭ የባላስቲክ ሚሳኤል ሙከራ ማድረጓን ተከትሎ በተፈጠረባቸው ሥጋት ነው፡፡

ይህ የሰሜን ኮሪያ የሚሳኤል ሙከራ በዚህ ዓመት ብቻ ለ 12ኛ ጊዜ የተደረገ ነው ተብሏል፡፡

ሰሜን ኮሪያ በዚህ ዓመት ጥር ወር ብቻ ሰባት አኅጉር አቋራጭ የሚሳኤል ሙከራ ማድረጓም ነው የተጠቆመው፡፡

ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.