የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ ከግድያ ሙከራ ተረፉ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ከግድያ መኩራ መትረፋቸው ተገለፀ።
ካርቱም ውስጥ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ባጀቡት ተሽከርካሪዎች ላይ ጥቃት መፈፁሙን የሀገሪቱ መንግስት ቴሌቪዥን ዘግቧል።

የሀገሪቱ ቴሌቪዥን በዘገባው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በአሁኑ ወቅት ደህንነቱ በተጠበቀ ስፍራ ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
ምንጭ፡- አረብ ኒውስ
ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision