የሐረሪ ክልል ካቢኔ የ2015 ረቂቅ በጀት ከ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ሆኖ እንዲጸድቅ ለክልሉ ምክር ቤት መራ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 13፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) በ2015 በጀት ዓመት የክልሉ መንግሥት ረቂቅ በጀት ከ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ ሆኖ እንዲጸድቅ ለክልሉ ምክር ቤት መርቷል፡፡
የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት በ2015 የበጀት ዓመት በጀት እና በሐረር ከተማ መዋቅራዊ ፕላን ላይ ተወያይቷል።
በውይይቱም በ2015 ዓ.ም የክልሉ መንግሥት ረቂቅ በጀት ከ3 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በላይ እንዲሆን ውሳኔ ማሳለፉን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡
ካቢኔው በክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ የቀረበለትን የ2015 የበጀት ዓመት ረቂቅ በጀት መርምሮ ለክልሉ ምክር ቤት መርቷል።
በጀቱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ14 በመቶ ጭማሪ እንዳለው ተገልጿል፡፡