የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ካይሮ ገቡ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 17፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌይ ላቭሮቭ ለይፋዊ የስራ ጉብኝት ግብፅ ካይሮ ገብተዋል፡፡
የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ እንዳስታወቁት ፥ ላቭሮቭ በካይሮ ቆይታቸው ከግብፅ ባለስልጣናት ጋር ይመክራሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ላቭሮቭ የአፍሪካ ጉብኝታቸውን በይፋ የጀመሩ ሲሆን ፥ በቀጣይም በኢትዮጵያ፣ በኡጋንዳ እና በዲሞከራቲክ ኮንጎ የስራ ጉብኝት እንደሚያከናውኑ ሲጂቲኤን አፍሪካ ዘግቧል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!