1ሺህ 29 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 29 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመለሱ፡፡
ለተመላሽ ዜጎች ተገቢው ድጋፍ እና እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት መሄዳቸው ተገልጿል፡፡
ዛሬ በሦስት ዙር ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው 1 ሺህ 29 ዜጎች መመለሳቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ጽህፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡
እስካሁን ድረስ በተከናወነ ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ 69 ሺህ 683 ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል፡፡