Fana: At a Speed of Life!

ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በኢትዮጵያ ከቻይና አምባሳደር ጋር መከሩ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 28 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሐረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ በኢትዮጵያ ከቻይና አምባሳደር ዣኦ ዚዩዋን ጋር ተወያይተዋል፡፡

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ ፥ በክልሉ ለተገኙት አምባሳደር የእንኳን ደህና መጡ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ፥ የክልሉን አስደናቂ ቅርሶችንም አስጎብኝተዋቸዋል።

አምባሳደሩ የዓለም ቅርስ የሆነውን የሐረር ጁገልን የጎበኙ ሲሆን ፥ በጋራ ጉዳዮች ላይም ፍሬያማ ውይይት ማድረጋቸውን የክልሉ መንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ አመላክቷል።

በቀጣይም ሁለገብ ግንኙነቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ያላቸውን ምኞት ገልፀዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.