አፍሮ የኬሚካልና ስቲል ማምረቻ 100 ሺህ ጥንድ የእጅ ጓንቶች ለጤና ሚኒስቴር አበረከተ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) አፍሮ የኬሚካልና ስቲል ማምረቻ አክሲዮን ማህበር 100 ሺህ ጥንድ የእጅ ጓንቶች ለጤና ሚኒስቴር አበርክቷል።
ማህበሩ የእጅ ጓንቶቹን ለጤና ሚኒስቴር ያበረከተው የኮሮናቫይረስ በሽታን መከላከልና መቆጣጠር የሚደረገው ስራ ለማገዝ መሆኑንም ተገልጿል።
በዚህም መሰረት አፍሮ የኬሚካልና ስቲል ማምረቻ አክሲዮን ማህበር በውስጡ 100 ሺህ ጥንድ ጓንቶች ን የያዘ 1 ሺህ ካርቶን የእጅ ጓንት ማበርከቱን ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡