Fana: At a Speed of Life!

ክልል አቀፍ የ2015 የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር በሲዳማ ክልል ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)ክልል አቀፍ የአረንጓዴ ዐሻራ ማስጀመሪያ መርሐ ግብር “ነገን ዛሬ እንትከል” በሚል መሪ ሐሳብ በሲዳማ ክልል ዳራ ኦቲሊቾ ወረዳ ሾኢቾ ቀበሌ ተካሄደ፡፡

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር ተስፋዬ በልጅጌ፣ በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አብርሃም ማርሻሎ እና በም/ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የኦሮሚያ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባበሪ አብዱርሃማን አብደላ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል፡፡

በተጨማሪም የአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው ጀንበር (ዶ/ር)፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዮሐንስ ጫላ እንዲሁም የፌደራል እና የሲዳማ ክልል በየደረጃው የሚገኙ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

በብርሃኑ በጋሻው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.