ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የንግድ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ከእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የንግድ ሚኒስትር ኒገል ሃድልስተን ጋር ተወያይተዋል፡፡
የገንዘብ ሚኒስትር ዴዔታው ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ÷በሁለቱ ሀገራት ያለውን የቆየ ወዳጅነት አንስተው÷ ስለተዘጋጀው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ረቂቅ ላይ ገለጻ አድርገዋል፡፡
የእንግሊዝ ዓለም አቀፍ የንግድ ሚኒስትር ኒገል ሃድልስተን በበኩላቸው÷የሀገራቸው መንግስት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን የኢንቨስትመንትና የንግድ ግንኙነት ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆኑን አረጋግጠዋል፡፡