Fana: At a Speed of Life!

በክረምቱ ወራት 108 ሺህ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ መታቀዱ ተጠቆመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በክረምቱ ወቅት እንደሀገር 108 ሺህ ዩኒት ደም ለመሰብሰብ መታቀዱን የኢትዮጵያ ደምና ኅብረ ሕዋስ ባንክ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ታዬ ተናገሩ፡፡

የክረምት የበጎ ፈቃድ ደም ልገሳ መርሐ ግብር ማስጀመሪያ በአዳማ ከተማ መካሄዱን የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

በመርሐ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ ንግግር ያደረጉት አቶ ሀብታሙ ታዬ÷ ሁሉም አካላት ለዕቅዱ ስኬት በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የክረምት እና የጾም ወቅቶች የደም እጥረት እንደሚከሰትባቸው ጠቁመው÷ በደም እጥረት ሊከሰት የሚችለውን ሞት ለመቀነስ ሁኔታዎች የሚፈቅዱለት ሁሉ ደም እንዲለግስ ጠይቀዋል፡፡

#Ethiopia

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/

ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.