Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል የፊታችን ሐምሌ 11 ከ260 ሚሊየን በላይ ቸግኞች ይተከላሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የፊታችን ሐምሌ 11 ቀን 2015 ዓ.ም ከ260 ሚሊየን በላይ ቸግኞች በአንድ ጀምበር እንደሚተከሉ የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡

የክልሉ ግብርና ቢሮ የተፈጥሮ ሐብት ጥበቃና አጠቃቀም ዳይሬክተር እስመለዓለም ምሕረት ÷ በደቡብ ጎንደር ፣ ምዕራብ ጎጃም ፣ ምዕራብ ጎንደር ዞኖች እና ደሴ ከተማ አስተዳደር ምዕራፍ ሁለት የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር ተጀምሯል ብለዋል፡፡

እስካሁንም ግማሽ ሚሊየን ችግኞች መተከላቸውን ነው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የተናገሩት፡፡

በክረምቱ ወቅትም እንደክልል 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ችግኞችን ለመትከል መታቀዱን አመላክተዋል፡፡

በታለ ማሞ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.