Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ሕይወታቸውን ላጡ በ’ሌኒንግራድ ጀግኖች ተከላካዮች መታሰቢያ ሐውልት’ የአበባ ጉንጉን አኖሩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 19፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት ሕይወታቸውን ላጡ በ’ሌኒንግራድ ጀግኖች ተከላካዮች መታሰቢያ ሐውልት’ ላይ የአበባ ጉንጉን አኖሩ፡፡

ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ (ዶ/ር) በሁለተኛው የሩሲያ-አፍሪካ የመሪዎች ጉባዔ ለመሳተፍ ሩሲያ-ቅዱስ ፒተርስበርግ ከተማ መግባታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

“ለሰላም ደኅንነትና ልማት” በሚል መሪ ሐሳብ በሚካሄደው ጉባዔ ላይ 49 የአፍሪካ ሀገራት ይሳተፋሉ፡፡

ለሁለት ቀናት የሚቆየው ጉባዔ ዓላማም÷ የሩሲያ-አፍሪካን ትብብር ማሳደግ መሆኑ ተመልክቷል፡፡

በተጨማሪም የአፍሪካ መንግስታትን ሉዓላዊነት ማጠናከር የጉባዔው ዓላማ ስለመሆኑ ተገልጿል፡፡

ከጉባዔው ጎን ለጎንም የሩሲያ እና አፍሪካን ኢኮኖሚያዊ እና ሰብዓዊ ጉዳዮች የሚመለከቱ ፎረሞች ይደረጋሉ ነው የተባለው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.