Fana: At a Speed of Life!

የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት 6ኛ የምርጫ ጊዜ 2ኛ የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ መካሄድ ጀምሯል፡፡

ጉባኤው በሁለት ቀናት ቆይታው የ2015 በጀት የአስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች፣ የኦዲት፣ የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ ቤትና የም/ቤቱን እቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያዳምጣል።

በተጨማሪም የ2016 የክልሉን የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድና የማስፈጸሚያ በጀት መርምሮ እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል፡፡

ጉባኤው በአዋጆችና በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በመወያየት ውሳኔዎችን እንደሚያሳልፍም የክልሉ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.