የጋምቤላ ክልል ም/ቤት ለክልሉ መንግስት የቀረበውን የ5 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጸደቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት ለክልሉ መንግስት ለ2016 ዓ.ም የቀረበውን የ5 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር በላይ በጀት አጽድቋል።
ምክር ቤቱ ለሁለት ቀናት ሲያካሄደው የቆየውን አራተኛ መደበኛ ጉባኤ ዛሬ አጠናቋል።
ምክር ቤቱ ለአዲሱ በጀት የልማት እና መልካም አስተዳደር እቅድ ማስፈጸሚያ የቀረበለትን 5 ቢሊየን 330 ሚሊየን ብር በጀት አፅድቋል።
ከፀደቀው በጀት መካከል 2 ቢሊየን 367 ሚሊየን ከክልል የተለያዩ የገቢ ምንጮች እንዲሁም ቀሪው 2 ቢሊየን 963 ሚሊየን ብር ደግሞ ከፌደራል መንግስት በድጎማና ሌሎች አማራጮች የሚሸፈን መሆኑ እንደተገለጸ ኢዜአ ዘግቧል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!