Fana: At a Speed of Life!

የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል ከ22 ድርጅቶች ጋር ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች ጋር ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን በጋራ ለመከላከል የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረመ።

ስምምነቱን የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ኃላፊ ተክሌ በዛብህ ከ22 ተቋማት ኃላፊዎች ጋር ነው የተፈራረሙት።

ዓላማውም ህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የተሻለ ቅንጅታዊ አሰራር እንዲኖር እንዲሁም ለተጎጂዎች የሚሰጡ አገልግሎቶች በተሻለ አግባብ ማቅረብ ይቻል ዘንድ ነው ተብሏል።

አቶ ተክሌ በዛብህ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት ፥ ህገወጥ የሰዎች ዝውውር የሀገራት የደህንነት ስጋት እየሆነ መጥቷል።

በርካታ ወንጀሎች በህገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር እንደሚፈጸም ገልጸው ፥ ይህንን ለመከላከል በቅንጅት መስራት እንደሚገባ ማስገንዘባቸውን የዘገበው ኢዜአ ነው።

እስካሁን መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ዘርፈ ብዙ ስራዎች መስራታቸውን ሲናገሩ ፥ አሁንም ከወትሮው የተለየ ቅንጅት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።

ዛሬ ከ22 ድርጅቶች ጋር የተደረገው ስምምነት በዘርፉ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች እንዲጠናከሩ እንደሚያግዝም ነው የተናገሩት።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.