Fana: At a Speed of Life!

አክሱም፣ ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል አክሱም፣ ዓዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎች የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎችን ተቀብለዋል።

 

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ኪሮስ ግዑሽ (ዶ/ር) ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደተናገሩት፥ ተማሪዎቹ የማጠናከሪያ እና የማካካሻ ትምህርት እየተሰጣቸው ነው።

 

የመቐለ ዩኒቨርሲቲም በቀጣዮቹ ሶስት ቀናት ተማሪዎችን መቀበል እንደሚጀምርም ተናግረዋል።

 

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በትግራይ ክልል በ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና መውሰድ ሲገባቸው ያልወሰዱ ተማሪዎች በቀጣይ ፈተና ላይ እንደሚቀመጡ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

 

በክልሉ በቀጣይ መስከረም ወር የመልቀቂያ ፈተና እንደሚሰጥም ትናንት በሰጡት መግለጫ አንስተዋል።

 

 

 

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.