ሜታ ኩባንያ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አመራሮች ስልጠና ሰጠ
ሜታ ኩባንያ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አመራሮች ስልጠና ሰጠ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሜታ ኩባንያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አመራሮችና ሰራተኞች ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ስልጠናው ኩባንያው በፌስቡክ፣ በዋትስ አፕና በኢንስታግራም የሰው ሰራሽ አስተውሎትን በመጠቀም ያካበተውን ተሞክሮ ለኢንስቲትዩቱ ለማጋራት እና አብሮ ለመስራት የሚያስችል ነው ተብሏል፡፡
ስልጠናው በዘርፉ የላቀ እውቀት እና ክህሎት ያላቸውን የመስኩ ምሁራን በመላክ የተሰጠ መሆኑን የኢንስቲትዩቱ መረጃ ያመላታክል፡፡