Fana: At a Speed of Life!

ጤና ሚኒስቴርና ዩኤንኤፍፒኤ በሰብዓዊ ምላሽ ላይ ያላቸውን ትብብር ለማሳደግ ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጤና ሚኒስቴር እና የመንግሥታቱ ድርጅት የሥነ-ሕዝብ ፈንድ (ዩኤንኤፍፒኤ) በሰብዓዊ ምላሽ እና ሌሎች ዘርፎች ያላቸውን ትብብር ይበልጥ ለማሳደግ ተስማምተዋል፡፡

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጀ ዱጉማ ከመንግሥታቱ ድርጅት የሥነ-ሕዝብ ፈንድ ሰብዓዊ ምላሽ ዳይሬክተር ሾኮ አራካኪ እና የድርጅቱ የኢትዮጵያ ተወካይ ኮፊ ኩዋሜ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷ ጤና ሚኒስቴርና ዩኤንኤፍፒ በትብብር መስራት በሚችሉባቸው ጉዳዮች ላይ ፍሬያማ ምክክር መደረጉን ሚኒስትር ዴኤታው በማሕበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ተቋማቱ በአደጋ እና ሰብዓዊ ምላሽ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ይበልጥ እንዲያሳድጉ ስምምነት ላይ መደረሱንም ጠቁመዋል፡፡

 

 

#Ethiopia

 

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/

ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting

ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/

ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision

ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/

ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.