Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያና ብሪክስ መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን የሚያጠናክር ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 30፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያና ብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡

በሕንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር ደመቀ አጥናፉ ከብሪክስ ንግድና እና ኢንዱስትሪ ም/ቤት መስራች ማዱካር (ዶ/ር) እና ምክትል መስራች ሱሺ ሲንግ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም÷በኢትዮጵያና በብሪክስ አባል ሀገራት መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መክረዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም በኢትዮጵያና በብሪክስ መካከል የንግድ እና ኢንቨስትመንት ትስስርን ማሳደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.