Fana: At a Speed of Life!

ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ከፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 22፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) ከኡጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ ጋር ተወያዩ፡፡

በውይይታቸው ሁለቱ ወገኖች በቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ ያላቸውን የሁለትዮሽ ትብብር ማሳደግ በሚችሉባቸው ሁኔታዎች ላይ ምክክር አድርገዋል፡፡

በተጨማሪም ሙላቱ ተሾመ (ዶ/ር) በኡጋንዳ ፕሬዚዳንት ፅህፈት ቤት ተገኝተው ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተላከውን ልዩ መልክት ለፕሬዚዳንት ሙሴቬኒ ማድረሳቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.