Fana: At a Speed of Life!

በ2 ነጥብ 3 ሔክታር መሬት ላይ የተገነባው ኮልፌ የግብርና ምርቶች መሸጫ የገበያ ማዕከል ነገ ይመረቃል

 

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 23 ፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2 ነጥብ 3 ሔክታር መሬት ላይ የተገነባው ኮልፌ የግብርና ምርቶች መሸጫ የገበያ ማዕከል በነገው ዕለት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በተገኙበት ይመረቃል::

በከተማው የሚስተዋለውን የዋጋ ንረት ለማረጋጋትና አምራችን ከሸማች ጋር በቀጥታ ለማገናኝት ከተማ አስተዳደሩ የግብርና ምርት መሸጫ ማዕከላትን እያስገነባ ይገኛል፡፡

በዚህም በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ በ2 ነጥብ 3 ሔክታር መሬት ላይ የተገነባውና 4 ህንፃ ያሉት የኮልፌ የግብርና ምርቶች መሸጫ የገበያ ማዕከል ፕሮጀክት ግምባታ ተጠናቆ በነገው ዕለት ተመርቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.