የድህረ ምረቃ ተማሪዎች መግቢያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ከነገ ጀምሮ ይሰጣል
አዲስ አበባ፣ ሕዳር 4፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)የድህረ ምረቃ ተማሪዎች መግቢያ ፈተና በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ2ኛ ጊዜ ነገ እና ከነገ በስቲያ እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
ፈተናው በ46 የፈተና ማዕከላት የሚሰጥ ሲሆን ÷ 9 ሺህ 70 ተማሪዎች ለመፈተን መመዝገባቸው ተመላክቷል፡፡
በዚህም ፈተናው ሕዳር 5 እና 6 2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡