Fana: At a Speed of Life!

“ስትራይድ ኢትዮጵያ 2024” አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዚዬም ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሣይንስ፣ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራ ላይ ትኩረቱን ያደረገው “ስትራይድ ኢትዮጵያ 2024” አውደ ርዕይ በሳይንስ ሙዚዬም ተከፈተ።

በአውደ ርዕዩ መክፈቻ ላይ የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስተር ዴዔታ ባይሳ በዳዳ(ዶ/ር) ጨምሮ የሚኒስቴሩ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች ተገኝተዋል።

በአውደ ርዕዩ የተለያዩ የፈጠራ ውጤቶች እና የቴክኖሎጂ ሥራዎች ለዕይታ ቀርበዋል።

ዛሬ በይፋ በሳይንስ ሙዚዬም የተከፈተው አውደ ርዕይ “ሣይንስ በር ይከፍታል ፤ ቴክኖሎጂ ያስተሳስራል ፤ ፈጠራ ወደ ፊት ያራምዳል” በሚል መሪ ሃሳብ እስከ መጪው ግንቦት 18 ቀን እንደሚቆይ ተመላክቷል።

በወንድሙ አዱኛ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.