Fana: At a Speed of Life!

ጠ/ሚ ዐቢይ ከካናዳ አቻቸው ጀስቲን ትሩዶ ጋር በስልክ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ከካናዳው ጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር በስልክ ተወያዩ።

ውይይቱን አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በፌስቡክ ገፃቸው ባወጡት መረጃ፥ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጀስቲን ትሩዶ ጋር በስልክ መወያየታቸውን አስታውቅዋል።

“በነበረን የስልክ ውይይት፣ የሁለቱን ሀገራት ሕዝቦች ከኮቪድ 19 በኋላ ለሚፈጠረው የዓለም ሁኔታ ለማዘጋጀት፣ ዓለም አቀፋዊ እና የተቀናጀ አመራር እጅግ አስፈላጊ እንደ ሆነ ተነጋግረናል” ብለዋል።

#FBC

የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.