Fana: At a Speed of Life!

በአውሮፓ ዋንጫ ጣልያን ከክሮሺያ ጥሎ ማለፉን ለመቀላቀል ተጠባቂ ጨዋታ ያደርጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 17፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ ዛሬ ጣልያን እና ክሮሺያ ጥሎ ማለፉን ለመቀላቀል የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡

በ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ምሽት 4 ሰዓት ላይ የምድብ ሁለት የመጨረሻ ጨዋታዎች ይደረጋሉ።

በዚህ መሰረትም ምሽት 4 ሰዓት ላይ ጣልያን እና ክሮሺያ ጥሎ ማለፉን ለመቀላቀል የሚያደርት ብርቱ ፉክክር ተጠባቂ ነው፡፡

ጣልያን በሁለቱ የምድብ ጨዋታዎች 3 ነጥብ በመያዝ 2ኛ ደረጃን ስትይዝ÷ ክሮሺያ ደግሞ 1 ነጥብ በመያዝ የምድቡ ግርጌ ላይ ተቀምጣለች፡፡

በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ አስቀድማ ወደ ጥሎ ማለፉ የተቀላቀለችው ስፔን በምድቡ ቀዳሚ ሆና ለማጠናቀቅ ከአልባኒያ ጋር የምትጫዎት ይሆናል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.