Fana: At a Speed of Life!

በሀዋሳ ከተማ የኮሪደር ልማት ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀዋሳ ከተማ ‘የኮሪደር ልማት ለላቀ ከተማችን ውበት” በሚል መሪ ቃል የከተማዋ ኮሪደር ልማት ስራ ተጀምሯል፡፡

በኮሪደር ልማት ስራው በከተማዋ በ1 ቢሊየን 64 ሚሊዮን ብር 11 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን የከተማዋ የኮሪደር ስራ ይከናወናል ተብሏል፡፡

በተጨማሪም ከዳቶ እና ጨፌ ሰፈሮች ወጣ ብሎ የሚገኘውን የ34 ነጥብ 2 ኪሎ ሜትር መንገድ 2 ቢሊየን 64 ሚሊዮን ብር ወጭ በማድረግ የመክፈት ስራ እንደሚከናወን ተጠቁሟል፡፡

የልማት ስራው የሳይክል፣ አረንጓዴ ስፍራ፣ መዝናኛና የህዝብ መፀዳጃ ስፍራዎችን ያካተተ ሆኖ በሶስት ምዕራፍ እንደሚጠናቀቅ ተመላክቷል፡፡

በመቅደስ አስፋው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.