Fana: At a Speed of Life!

በጌዴኦ ዞን በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የሟቾች ቁጥር 9 ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጌዴኦ ዞን ጮርሶ ወረዳ ዲባንድቤ ቀበሌ ሻይሳ አካባቢ ዛሬ ረፋድ 5 ሠዓት ላይ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ በአራት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደረሰ፡፡

አደጋው የተከሰተው “ሲኖ ትራክ” እየተባለ የሚጠራው የደረቅ ጭነት ተሽከርካሪ ከዲላ ወደ ሞያሌ ከሚጓዝ “ዶልፊን” የሕዝብ ማመላለሻ እና ከቡሌ ሆራ ወደ ዲላ ሲጓዝ ከነበር “ኤፍ ኤስ አር” ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው ተብሏል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.