Fana: At a Speed of Life!

የዘንድሮ የአረንጓዴ ዓሻራ ተካፋይ እንድትሆኑ ጥርዬን አቀርባለው – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ህብረተሰቡ የዘንድሮ የአረንጓዴ ዓሻራ መርሐ ግብር ተካፋይ እንዲሆን ጥሪ አቀረቡ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች ጋር በመሆን በጫካ ፕሮጀክት ሀገር በቀል የአረንጓዴ አሻራ ችግኞችን ተክለዋል።

ይህን ተከትሎም ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው፤ “የዘንድሮ የአረንጓዴ ዓሻራ ተካፋይ እንድትሆኑ ጥርዬን አቀርባለው” ብለዋል፡፡

የባህር ዛፍን በሀገር በቀል የዛፍ ዝርያዎች የመተካቱ ሂደት ተጠናክሮ መቀጠሉንም ነው ከጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክተው፡፡

 

 

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.