ለጎፋ ዞን 4 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ድጋፍ ተደረገ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 26፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር በጎፋ ዞን በመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች የሚውል 4 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ዋጋ ያለው የዓይትና የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረገ፡፡
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) በአደጋው በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸው÷ 2 ሚሊየን ብር በጥሬ ገንዘብ እና 2 ነጥብ 6 ሚሊየን ብር ዋጋ ያለው የዓይነት ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል፡፡
ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ መግለጻቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጽ/ቤት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡
በተመሳሳይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በመሬት መንሸራተት ጉዳት ለደረሰባቸው የሚውል አምስት ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል።
የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሽፈራው ተሊላ ድጋፉን ባስረከቡበት ወቅት ÷ በመልሶ ማቋቋም ሥራውም አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርጋለን ብለዋል፡፡