Fana: At a Speed of Life!

ሚኒስቴሩ ለጎፋ ዞን 6 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር የሚገመት ድጋፍ አደረገ

 

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ሚኒስቴር በጎፋ ዞን በደረሰው የመሬት መንሸራተት አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች ከ6 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የአይነትና የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል፡፡

ከተደረገው ድጋፍ ውስጥ 2 ነጥብ 2 ሚሊየን ብሩ በጥሬ ገንዘብ ሲሆን÷ 4 ነጥብ 2 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመተው ደግሞ በአይነት መሆኑ ተገልጿል።

የሰላም ሚኒስትር ብናልፍ አንዷለም በአደጋው በደረሰው ጉዳት የተሰማቸውን ሃዘን ገልጸው÷ድጋፉን ለክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ አስረክበዋል፡፡

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በቀጣይ በአደጋው የተጎዱ ወገኖችን ለማቋቋምና ለመደገፍ የተለያዩ አካላትን በማስተባበር የ30 ሚሊየን ብር ድጋፍ እንደሚያደርግ መናገራቸውንም የርዕሰ መስተዳድሩ ጽ/ቤት መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.