Fana: At a Speed of Life!

አቶ እንዳሻው ጣሰው እና ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የወራቤ ንጹሕ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው እና የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) የወራቤ ንጹህ መጠጥ ውሃና ሳኒቴሽን ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል፡፡

በጉብኝቱ ወቅት የፕሮጀክቱ ተቋራጭ ÷ፕሮጀክቱ 80 ኪሎ ሜትር የመስመር ዝርጋታ እንደሚኖረው እና 60 ሺህ ሰዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ኤሌክትሮ ሜካኒካል እቃዎች በመግባት ላይ መሆናቸውን ጠቁመው÷ የመብራት ተከላ ሥራ እየተከናወነ እንደሚገኝም ጠቅሰዋል፡፡

የፕሮጀክቱ የውሃ ጉድጓዶች እስከ 20 ዓመት አገልግሎት መስጠት እንደሚችሉ ነው የተመላከተው፡፡

የፕሮጀክቱን ግንባታ በ1 ዓመት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እንደሚሰራም የፕሮጀክቱ ተቋራጭ ገልጸዋል፡፡

በኤርሚያስ ቦጋለ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.