Fana: At a Speed of Life!

የተማሪዎችን ውጤትለማሻሻል የትምህርት ማህበረሰቡ የበኩሉን ሊወጣ ይገባል – አቶ አሻድሊ ሃሰን

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 12፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የተማሪዎችን ውጤትና ሥነምግባር ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት የትምህርት ማህበረሰቡ የበኩሉን ሚና ሊወጣ ይገባል ሲሉ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሃሰን ገለጹ።

አቶ አሻድሊ የተማሪዎችን ውጤትና ሥነ-ምግባር ማሻሻል በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ በየደረጃው ከሚገኙ የትምህርት አመራሮችና ርዕሳነ-መምህራን ጋር መክረዋል፡፡

ርዕሰ መስተዳድሩ በዚህ ወቅት÷ ባለፉት ዓመታት በትምህርቱ ዘርፍ ያጋጠሙትን ስብራቶች ለመጠገን በርካታ ተግባራት ተሰርቷል ብለዋል።

በክልሉ በነበረው የፀጥታ ችግር ጫና ውስጥ ከነበሩት ተቋማት የትምህርቱ ዘርፍ አንዱ መሆኑን ጠቁመው÷ ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የወደሙ የትምህርት ተቋማትን በመልሶ በማቋቋም የተዘጉ ት/ቤቶች እንዲከፈቱ መደረጉን ጠቅሰዋል።

በክልሉ አብዛኛው የትምህርት ተቋማት ከደረጃ በታች መሆናቸው ለትምህርት ጥራቱ ችግር መሆኑን ያነሱት አቶ አሻድሊ÷ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል።

ወቅቱ የሚጠይቀውን ብቁ እና ተወዳዳሪ ዜጋን ለመፍጠር በሚደረገው ጥረት የትምህርት አመራሩ እና ማህበረሰብ የበኩሉን ሊወጣ እንደሚገባም አቶ አሻድሊ አሳስበዋል።

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.