Fana: At a Speed of Life!

19ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በስኬት ተከብሮ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 19ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ቀን በዓል በአርባ ምንጭ ከተማ በስኬት ተከብሮ መጠናቀቁን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አስታወቀ፡፡

የክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ሃላፊ ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን በሰጡት መግለጫ÷19ኛው የብሔሮች ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓል ከሕዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በአርባ ምንጭ በተለያዩ ዝግጅቶች ሲከበር መቆየቱን አንስተዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የበዓሉ ማጠቃለያ መርሐ ግብር በስኬት ተከብሮ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

በዓሉ በስኬት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ የአርባምንጭ ከተማና አከባቢዋ ነዋሪዎች እንዲሁም የጸጥታ አካላት ላበረከቱት አስተዋፅኦም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.