Fana: At a Speed of Life!

ዓለም አቀፉ የፀረ-ሙስና ቀን የማጠቃለያ መድረክ ፕሬዚዳንት ታዬ በተገኙበት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 2፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተገኙበት 21ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን የማጠቃለያ መድረክ በአዲስ አበባ የዓድዋ ድል መታሰቢያ እየተካሄደ ነው።

በመርሐ ግብሩ ላይ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ በሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ እውነቴ አለነ፣ የምክር ቤት አባላት፣ የፌደራል የሥነ-ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር ሳሙኤል ኡርቃቶ (ዶ/ር)፣ ሚኒስትሮች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ታድመዋል።

21ኛው ዓለም አቀፍ የፀረ-ሙስና ቀን “ወጣቶችን ያማከለ የፀረ-ሙስና ትግል የነገን ስብዕና ይገነባል” በሚል መሪ ሃሳብ ሲካሄድ መቆየቱ ይታወቃል።

በመድረኩ ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን በ2016 ዓ.ም ሙስናን በመታገል ላበረከተው አስተዋጽኦ እውቅና ተሰጥቶታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.