በኦሮሚያ ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ጥር 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኦሮሚያ ክልል የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ዘመቻ መጀመሩን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡
በመርሐ ግብሩ 3 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር መሬት ላይ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራ ለማከናወን መታቀዱን ተመላክቷል፡፡
በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራውን በስኬት ለማከናወን 9 ነጥብ 9 ሚሊየን በላይ ዜጎች ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
የተፈጥሮ ሃብት ልማትና ጥበቃ ሥራ የሚከናወንባቸው ተፋሰሶች የተለዩ ሲሆን÷በመርሐ ግብሩ 9 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር የሚገመት ሥራ እንደሚሰራ ይጠበቃል፡፡