Fana: At a Speed of Life!

7 ድርጅቶች በድሬዳዋ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የመስሪያ ቦታ ተረከቡ

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በድሬዳዋ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን ውስጥ ተሰማርተው የንግድ ሥራ ለማከናወን ማመልከቻ ያስገቡና ተመርጠው ወደ ሥራ ለሚገቡ 7 ድርጅቶች የቦታ ርክክብ ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ÷ በዛሬው ዕለት በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ ውስጥ ቦታ ተረክባችሁ ሥራ ለጀመራችሁ የንግዱ ማህበረሰብ አባላት እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡

ነሐሴ 2014 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ ተመርቆ ሥራ የጀመረው ነጻ የንግድ ቀጣናው በተለያዩ ተቋማት ቅንጅት አስፈላጊው የቅድመ ዝግጅት ሥራ ተከናውኖ የኦፕሬሽን ሥራው በመሳለጥ ላይ እንደሚገኝ ተመላክቷል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.