Fana: At a Speed of Life!

በ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የብረት ፋብሪካ ሊገነባ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ከተማ በ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ወጪ ለሚገነባው የቶሚ ብረት ማምረቻ ፋብሪካ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ ተቀምጧል።

 

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ የመሰረት ድንጋዩን ባስቀመጡበት ወቅት÷የክልሉ መንግስት ለፋብሪካው ባለቤቶች አስፈላጊዉን ድጋፍ እና እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

 

የሚገነባው የብረታ ብረት ፋብሪካ ለግንባታ የሚሆን ብረቶችን በጥራት በማምረት በኩል የጎላ አስተዋፅኦ ለማበርከት እንደሚያስችል መገለፁን የክልሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.