ጠ/ ሚ ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢኳቶሪያል ጊኒ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከ38ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ከኢኳቶሪያል ጊኒ ፕሬዚዳንት ኦቢያንግ ኑጌሚያ ባሶንጎጋር ተወያይተዋል፡፡
በውይይታቸው ሁለቱ ሀገራት ቁልፍ በሆኑ ዘርፎች አጋርነታቸውን ለማጠናከር በሚችሉበት መንገዶች ላይ መምከራቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡
ለጋራ ዕድገትና ብልጽግናም ትብብራቸውን ለማጠናከርም ተስማምተዋል፡፡