Fana: At a Speed of Life!

አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) የኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪግ ኢንዱስትሪን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የመከላከያ ሚኒስትር አይሻ መሃመድ (ኢ/ር) በመከላከያ ኢንጅነሪግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ስር የሚገኘውን የኤሌክትሮኒክስ ኢንጅነሪግ ኢንዱስትሪ ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም የመከላከያን ፍላጎት ለማሳካት ኢንዱስትሪው የሚያመርታቸውን የአጭር፣ መካከለኛና ረጅም ርቀት ራዲዮኖችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

ሚኒስትሯ በዚህ ወቅት÷የተለያዩ ርቀት ያላቸው ራዲዮኖችን በራስ አቅም በማምረት መገጣጠም መቻላችን እንደ ሀገር ብሎም እንደተቋም ከፍተኛ አቅም እንዳለን ያሳያል ብለዋል፡፡

የተጀመረው ሥራ የሚያበረታታ መሆኑን ገልጸው÷በቀጣይ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በጉብኝቱ የመከላከያ ኢንጅነሪግ ኢንዱስትሪ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ሃይለማሪያምና የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች መሳተፋቸውን የመከላከያ ሰራዊት መረጃ ያመላክታል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.