ከተለያዩ የስፖርት ማኅበራት የተውጣጡ የስፖርት ቤተሰቦች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎበኙ
አዲስ አበባ፣ የካቲት 28፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከተለያዩ የስፖርት ማኅበራት የተውጣጡ የአዲስ አበባ የስፖርት ቤተሰቦች አዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ማዕከልን ጎብኝተዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይም፤ አሰጣልኞች፣ የእግር ኳስ ተጫዋቾች፣ የእግር ኳስ ደጋፊዎች እንዲሁም የተለያዩ ስፖርት ማኅበራት ተወካዮች ተሳትፈዋል፡፡
በዚሁ ወቅትም ማዕከሉ ሁለንተናዊ ፋይዳ እንዲሰጥ ታስቦ መገንባቱ እንዳስደሰታቸው መናገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡