አካዳሚው ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ወታደራዊ አካዳሚ የ70ኛ ዙር ቃኘው ኮርስ ዕጩ መኮንኖችን እያስመረቀ ነው፡፡
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላን ጨምሮ ጄኔራል መኮንኖች፣ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና ወታደራዊ አታሼዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
ተመራቂ ዕጩ መኮንኖቹ የሚጠበቅባቸውን ሥልጠና ወስደው ያጠናቀቁ መሆናቸው ተገልጿል፡፡
በአንዱዓለም ተስፋዬ