‘ቸርነት ሀሪፎ ማን ነው?
አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት ቸርነት ሀሪፎ በተባበሩት መንግሥታት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይ ሆኖ ተሹሟል፡፡
ለመሆኑ ይህ ወጣት ማን ነው….?
👉 በልጅነቱ ወደ ኬንያ ያቀናው ቸርነት ሀሪፎ፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በናይሮቢ ኪሊማኒ ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡
👉 ከዚያም ወደ አሜሪካ አምርቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በፔንስልቬንያ ሎወር ሜሪዮን ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡
👉 በትምህርት ቤቱ ባገኘው የትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) አማካኝነትም ቴምፕል ዩኒቨርሲቲን መቀላቀል ችሏል።
👉 ወጣቱ ዲፕሎማት በፖለቲካል ሣይንስና ሕግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአሜሪካው ቴምፕል ዩኒቨርሲቲ አግኝቷል።
👉 በአሁኑ ወቅትም በፔንስልቬንያ ዩኒቨርሲቲ የማስተርስ ዲግሪ ትምህርቱን በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን እየተከታተለ እንደሚገኝ በተባበሩት መንግሥታት ድረ-ገጽ ላይ የሰፈረው መረጃ ያመለክታል።
👉 ከአሁን ቀደም በተለይም በስደተኞችና በትምህርት ጉዳይ የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ በዓለም አቀፍ መድረኮች በንቃት ሲሳተፍ መቆየቱም ተጠቅሷል፡፡
👉 ይህ ዲፕሎማት ሥድስት ቋንቋዎችን ማለትም አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ስዋሂሊ፣ እንግሊዝኛ እና ፈረንሳይኛ አቀላጥፎ እንደሚናገር ገልጿል።
👉 ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት ቸርነት ሀሪፎ በተባበሩት መንግሥታት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይ ሆኖ ተሹሟል፡፡
👉 የሹመት ደብዳቤውንም ለመንግሥታቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አቅርቧል።
በኃይለማርያም ተገኝ