Fana: At a Speed of Life!

‘ቸርነት ሀሪፎ ማን ነው?

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት ቸርነት ሀሪፎ በተባበሩት መንግሥታት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይ ሆኖ ተሹሟል፡፡

ለመሆኑ ይህ ወጣት ማን ነው….?

👉 በልጅነቱ ወደ ኬንያ ያቀናው ቸርነት ሀሪፎ፤ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በናይሮቢ ኪሊማኒ ትምህርት ቤት ተከታትሏል፡፡

👉 ከዚያም ወደ አሜሪካ አምርቶ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በፔንስልቬንያ ሎወር ሜሪዮን ትምህርት ቤት ተምሯል፡፡

👉 በትምህርት ቤቱ ባገኘው የትምህርት ዕድል (ስኮላርሺፕ) አማካኝነትም ቴምፕል ዩኒቨርሲቲን መቀላቀል ችሏል።

👉 ወጣቱ ዲፕሎማት በፖለቲካል ሣይንስና ሕግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪውን ከአሜሪካው ቴምፕል ዩኒቨርሲቲ አግኝቷል።

👉 በአሁኑ ወቅትም በፔንስልቬንያ ዩኒቨርሲቲ የማስተርስ ዲግሪ ትምህርቱን በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን እየተከታተለ እንደሚገኝ በተባበሩት መንግሥታት ድረ-ገጽ ላይ የሰፈረው መረጃ ያመለክታል።

👉 ከአሁን ቀደም በተለይም በስደተኞችና በትምህርት ጉዳይ የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ በዓለም አቀፍ መድረኮች በንቃት ሲሳተፍ መቆየቱም ተጠቅሷል፡፡

👉 ይህ ዲፕሎማት ሥድስት ቋንቋዎችን ማለትም አማርኛ፣ ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ ስዋሂሊ፣ እንግሊዝኛ እና ፈረንሳይኛ አቀላጥፎ እንደሚናገር ገልጿል።

👉  ወጣቱ ኢትዮጵያዊ ዲፕሎማት ቸርነት ሀሪፎ በተባበሩት መንግሥታት የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት (ኢጋድ) ቋሚ ተወካይ ሆኖ ተሹሟል፡፡

👉  የሹመት ደብዳቤውንም ለመንግሥታቱ ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ አቅርቧል።

በኃይለማርያም ተገኝ

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.