አርሰናል ከኒውካስል ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 10፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ37ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ አርሰናል ኒውካስል ዩናይትድን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ተጠባቂ ነው።
ምሽት 12:30 በሚደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ የሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፏቸውን ለማረጋገጥ ጠንካራ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል።
ከዚህ ጨዋታ አስቀድሞ ቀን 10:15 ለሻምፒየንስ ሊግ ተሳትፎ በሚደረገው ፉክክር ውስጥ የሚገኘው ኖቲንግሃም ፎረስት ከሜዳው ውጭ ዌስትሃም ዩናይትድን ይገጥማል።
ኤቨርተን ከሳውዛምፕተን 8 ሰዓት እንዲሁም ሌስተር ሲቲ ከኢፕስዊች ታውን፣ ብሬንትፎርድ ከፉልሃም በተመሳሳይ 11 ሰዓት የሚደረጉ ጨዋታዎች ናቸው።