ኦስማን ዴምቤሌ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የፒኤስጂ የፊት መስመር ተጫዋች ኦስማን ዴምቤሌ የ2024/25 አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል፡፡
የ28 ዓመቱ ዴምቤሌ በውድድር ዓመቱ ባደረጋቸው 15 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች፤ 8 ጎል አስቆጥሮ 6 ለግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የዴምቤሌ አስተዋፅኦ የጎላ ነበር፡፡
ፒኤስጂ በፍፃሜው ኢንተርሚላንን 5 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒየን መሆኑ ይታወቃል፡፡
በፍፃሜው ጨዋታ ሁለት ጎል አስቆጥሮ አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ ያቀበለው ሌላኛው የፒኤሴጂ ተጫዋች ዱዌ የዓመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች በመባል መመረጥ ችሏል።