መቐለ 70 እንደርታ ሲዳማ ቡናን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ33ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር መቐለ 70 እንደርታ ሲዳማ ቡናን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
ቀን 9 ሠዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ቤንጃሚን ኮቴ የመቐለ 70 እንደርታ ማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል።
ረፋድ 3 ሠዓት በተካሄደው ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ስሑል ሽረን 5 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል።
የዕለቱ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሠዓት ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ይገናኛሉ።