ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባደረጉት ባለ አራት ክፍል ቃለ ምልልስ በክፍል ሦስት፤ ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል፡-
👉 የኢትዮጵያን ሰው፣ መሬት እና ሀብት ከጫፍ እስከ ጫፍ ደምረን መጠቀም አለብን።
👉 በደቡብ ኦሞ 145 ኪሎ ሜትር መስኖ ሠርተናል፤ ይህን በአግባቡ በማሽን ታግዞ መጠቀም ሀገራዊ የምግብ ሉዓላዊነትን ያሳልጣል፡፡
👉 ቆላ ማለት ብዙን ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ ክፍል ነው፤ በማሽን በቀላሉ መልማት እና ብዙ ምርት መስጠት የሚችል አካባቢ ነው፡፡
👉 አጋር (ሁለተኛ ዜጋ) የተባለውን ሠርዘን፤ ባለቤት እንዲሆን አድርገናል፤ መሬቱን ብቻ ሳይሆን ሰውንም ደምረነዋል፡፡
👉 ኢትዮጵያ በአፍሪካ አንደኛዋ ስንዴ አምራች ናት፤ ሁለተኛ አምራቿን ግብጽንም በሦስት እጥፍ ትበልጣታለች፡፡
👉 ምን ያህል መሬት እንደታረሰ በየአካባቢው ሂደን ማየት አይጠበቅብንም፤ ባለንበት ቦታ ሆነን በሳተላይት ምስል እንመለከታለን፡፡
👉 ወደ ጠቅላይ ሚኒስትርነት በመጣሁ ሰሞን እስከ 1 ቢሊየን ዶላር ስንዴ ከውጭ ለማስገባት ይወጣ ነበር፤ ባለፉት ሁለት እና ሦስት ዓመት ግን አንድ ብር ስንዴ ለማስገባት አላወጣንም፡፡
👉 ኢትዮጵያ በርካታ የተለያዩ ሀገራት ስደተኞችን እንደመያዟ የሚረዱ አካላት ስንዴ ሊልኩ ይችላሉ፤ ይህ ግን ለኢትዮጵያ የተላከ ዕርዳታ አይደለም፤ ለስደተኞች እንጂ፡፡
👉 የነቃ አስተሳሰብ ቅድሚያ ለሀገር ምርት ይሰጣል፤ ችግር ቢኖር እንኳ በሀገር ምርት መኩራት ይገባል፡፡
👉 የገበያ ሥርዓቱ ድክመት አለበት፤ በዚህም ድሃው እንዳይጎዳ መንግሥት በትኩረት እየሠራ ነው፡፡
👉 ምርታማነታችንን በሔክታር ለማሳደግ በቀጣይ መሥራት ይጠበቃል።
👉 በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ቆላ ላይ ከፍተኛ ሐብት አላት፤ የከርሰ እና ገጸ ምድር ውኃው፣ የዝናቡ ሁኔታ፣ ያልታረሰ መሬት መኖሩ … በቀጣይ አበክረን መሥራት አለብን፡፡
በዮሐንስ ደርበው